የቁርኣን ደረጃና ትሩፋቱ

የቁርኣን ደረጃና ትሩፋቱ

‹‹ቁርኣን ምናባቸውን ሲቀሰቅስ፣ስነምግባራቸውን ሲቀርጽ፣በመቶ ሚሊዮኖች የመቆጠሩ ሰዎችን አእምሮና እሳቤ ሲሞርድ ለአስራ አራት ምእተ ዓመታት በሙስሊሞች ትውስታ ውስጥ ተጠብቆ ኖሯል። ቁርኣን ከሁሉም ይበልጥ ገርና ቀለል ያለ፣ከሁሉም ይበልጥ ከውስብስብነት፣ከድፍንፍን ምስጢራት፣ከካህናዊ ጣዖታዊ ስርዓታት የጸዳ ዐቂዳን በሰው ልቦና ውስጥ በሰው ልቦና ውስጥ ይተክላል። የሙስሊሞችን የስነምግባርና የስልጣኔ ደረጃን ከፍ በማድረግ ረገድም ትልቁን ሚና ተጫውቷል። የማሕበራዊ አነዋነዋርና የማሕበረሰባዊ አንድነት ስርዓት መሰረቶችን የተከለላቸውም እርሱ ነው። የጤና አጠባበቅ ሕጎችን እንዲከብሩ አበረታቷል። አእምሮአቸውንም ከብዙ አፈተረቶችና ግምታዊ ቅዠቶች፣ከግፍና ከጭካኔ ነጻ አውጥቷል። የጫንቃ ተገዥዎችን ሁኔታዎችም አሻሽሏል። ግፉአን ተዋራጆች በነበሩት ልብ ውስጥም የክብርና የልዕልና መንፈስ ዘርቷል።››


Tags: