የሴት ደረጃ

የሴት ደረጃ
‹‹እስላም በዐረቦች አገር የሴትን ደረጃ ከፍ አድርጓል። ሴት ሕጻናትን ከነሕይወታቸው የመቅበርን ልማድ አስወግዷል። በፍርድ ሂደቶችና በንብረት ባለቤትነት መብት ወንድና ሴትን እኩል አድርጓል። ለሴቷ ሐላል በሆነ ሥራ ላይ የመሰማራት፣የመውረስና ሠርታ ያገኘችውን ሀብት በባለቤትነት እንዳሻት የማድረግ መብት ሰጥቷል። በዘመነ ጃህሊያ የዐረቦች ልማድ የነበረውን ሴቶችን ከሌላው ንብረት ጋር ከአባት ወደ ልጅ ማስተላፍን ያስቀረ ሲሆን፣የሴትን የውርስ ድርሻ የወንዱ ድርሻ ግማሽ አድርጎ ያለ ፍቃዳቸው እንዳይዳሩም ከልክሏል።››


Tags: