ተሸናፊ አሸናፊውን ማረከው!!

ተሸናፊ አሸናፊውን ማረከው!!
‹‹በመስቀል ጦርነቶች ተሸናፊው እስላም አሸናፊዎቹን ማርኳል። የዛገ ላቲናዊ ሕይወት ወደነበረው ወደ ክርስቲያኑ ዓለም ሕይወትም የስልጣኔ ዓይነቶችን አስገብቷል። በአንዳንድ ሰብአዊ እንቅስቃሴ መስኮች፣ለምሳሌ በኪነ ሕንጻ በመካከለኞቹ ክፍለ ዘመናት እስላማዊው ተጽእኖ በመላው የክርስቲያን ዓለም ስር የሰደደ ነበር። በሲስሊና በአንደሉስ ደግሞ ጥንታዊው ዐረባዊ ኢምፓይር በአዲሱ ምዕራባዊ መንግስት ላይ ያሳረፈው አሻራ ሰፊ፣ጥልቅና አጠቃላይ ነበር።››


Tags: